Contacts

Addis Ababa Lideta Subcity Woreda 04, House no 887

contact@nia.org.et

+ 251 911244073/911 210535
648272039_911498241637340_2010984043964901194_n
EventsNews

Ethiopian Health Ministers Honor Nia Foundation on World Birth Defects Day

On World Birth Defects Day, Nia Foundation was honored with three distinguished awards across different categories by the Ethiopian Ministry of Health.

This recognition celebrates the pioneering work of the Joy Center for Autism, which has expanded opportunities for participation, care, and advocacy for children and youth with autism in Ethiopia.
Under the leadership of the Ministry of Health, Nia Foundation’s impact has extended beyond Addis Ababa—bringing awareness campaigns, training, and family support programs to regional communities including Mekele, Dire Dawa, Asela, Wolaita Sodo, Butajira, and Debre Berhan. These efforts have also inspired global partners to join the movement for equity and inclusion.
A special honor was given to Zemi and Yenus, paying tribute to their legacy and to the unwavering commitment of staff, board members, advisors, and families who have transformed challenges into strength. Their vision continues to guide the mission of uniting children, youth, and caregivers under Nia Foundation’s banner.
“This recognition is not ours alone,. “It belongs to every child and family striving for inclusion. It is a call to strengthen our commitment, expand awareness across nations, and ensure that no child is ever left behind.”

9Y4A5566
EventsNews

የአፈጣጠር ዕክል (Birth Defect) ሳምንት በአሰላ

ፋውንዴሽን-ጆይ ኦቲዝም ማዕከል ከጤና ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር “የላቀ ተደራሽነትን ለኢትዮጵያ ልጆች ፣ በመከላከል ፣ በሕክምና እና በማካተት እናረጋጥ!” በሚል መሪ መልዕክት ዓመታዊ የአፈጣጠር ዕክል (Birth Defect) ሳምንት በማስመልከት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን አሰላ ከተማ የኒውሮደቨሎፕመንታል ዲስኦርደር ልየታ እና መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ባለድረሻ አካላት የተዘጋጀ ወርክሾፕ

_Y4A5109
EventsNews

Nia Foundation-Joy Centre for Autism Celebrated Birth Defects week In Debrebrehan City



The Ministry of Health has officially launched the National Birth Defect Week under the guiding message, “Prevent, Care, Include: Advancing Equity for All Children in Ethiopia.” In alignment with this national call, the Nia Foundation–Joy Center for Autism organized a high-level stakeholder workshop in partnership with the Ministry of Health and the Amhara Regional Health Bureau to strengthen coordinated action on neurodevelopmental disorders.    

The workshop brought together key governmental and non-governmental stakeholders, including the Semien Shewa Zone Health Office, Women, Children and Social Affairs Offices, Education Offices, Debre Berhan City Health Office, Debre Berhan University (Department of Psychology and Health Faculty – Asrat Woldeyes Campus), Hakim Gizaw Hospital, Health Science College, Comprehensive Hospital, health centers, Ayu Hospital, different NGOs, Aste-Zereyakon Primary School, Parents, and other Partners. The strong multisectoral representation reflected a shared commitment to advancing inclusive and equitable services.

Opening the event, Mr. Bekele Gebrie, Head of the Debre Berhan City Health Office, emphasized the importance of early prevention, timely care, and social inclusion for children affected by birth defects and neurodevelopmental conditions. He highlighted the national responsibility to strengthen awareness, improve service coordination, and ensure that no child is left behind. He further stressed the need to institutionalize developmental screening and early identification within primary health care services to reduce delayed diagnosis and missed intervention opportunities. In addition, he called for stronger collaboration among health, education, and social sectors to build an inclusive support system that empowers families and promotes the full participation of children with disabilities in society.   

The workshop featured different expert presentations and interactive discussions focusing on awareness creation, advocacy, care systems, and inclusive service provision. Participants underscored the critical role of integrated, multisectoral collaboration in addressing neurodevelopmental disorders and reaffirmed their commitment to building coordinated and sustainable support systems for children and families in the community.   

የጤና ሚኒስቴር “የላቀ ተደራሽነትን ለኢትዮጲያ ልጆች፤ በመከላከል፣ በሕክምና፣ እና በማካተት እናረጋግጥ!” በሚል መሪ መልእክት ብሔራዊ የፈጣጠር እክል ሳምንትን በይፋ አስጀምሯል። ይህንንም ብሔራዊ ጥሪ በማስመልከት ኒያ ፋውንዴሽን-ጆይ ኦቲዝም ማዕከል ከጤና ሚኒስቴር እና ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ኒውሮደቨሎፕመንታል ችግሮችን በተመለከተ የተቀናጀ እርምጃን ለማጠናከር ከፍተኛ ደረጃ ያለው የባለድርሻ አካላት ወርክሾፕና ውይይት አካሂዶአል።    

ወርክሾፕና ውይይቱ ቁልፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የሴሚን ሸዋ ዞን የጤና መምሪያ፣ የሴቶች፣ የህፃናት እና የማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ፣ የትምህርት መምሪያ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ የጤና መምሪያ፣ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ (የስነ-ልቦና ድፓርትመንት ፣ የጤና ፋኩልቲ መምሪያ – አስራት ወልዴይስ ካምፓስ)፣ የሃኪም ግዛው ሆስፒታል፣ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ አጠቃላይ ሆስፒታል፣ የጤና ማዕከላት፣ አዩ ሆስፒታል፣ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የአፄ-ዘረ-ያዕቆብ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ወላጆችንና ሌሎች አጋር አካላትንም ያካተተ ነበረ። ጠንካራው ባለብዙ ዘርፍ ውክልና አካታች እና ፍትሃዊ አገልግሎቶችን ለማራመድ የጋራ ቁርጠኝነትን ያንፀባርቃል።    

ዝግጅቱን በመክፈቻ ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ የጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ፣ በአፈጣጠር ዕክል እና በኒውሮደቨሎፕመንታል ዲስኦርደር ለተጎዱ ህጻናት የቅድመ መከላከል፣ ወቅታዊ እንክብካቤ እና የማህበራዊ ተሳትፎ  እና የማካተት አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት ሰጥተዋል። ግንዛቤን ለማጠናከር፣ የአገልግሎት ቅንጅትን ለማሻሻል እና አንድም ልጅ እንዳይቀር ለማረጋገጥ ብሔራዊ ኃላፊነትን አጉልተው ገልጸዋል። በተጨማሪም በጊዜ በመለየትና ተገቢ አገልግሎቶችን በማቅረብ የማገገምና የመብቃት ዕድልን የመፍጠር ሥራን ተቋማዊ ስለማድረግ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም፣ ቤተሰቦችን የሚያበረታታ እና የአካል ጉዳተኛ ህጻናት በኅብረተሰቡ ውስጥ ሙሉ ተሳትፎን የሚያበረታታ ሁሉን አቀፍ የድጋፍ ስርዓት ለመገንባት በጤና፣ በትምህርት እና በማህበራዊ ዘርፎች መካከል ጠንካራ ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።   

ወርክሾፕና ውይይቱ በግንዛቤ ፈጠራ፣ በእንክብካቤ ስርዓቶች ፣ ስለምብታቸው መቆም እና አካታች የአገልግሎት አቅርቦት ላይ ያተኮሩ የተለያዩ የባለሙያ አቀራረቦች መልዕክት ተላልፎአል ፤ ውይይቶችን ተደርገዋል። ተሳታፊዎች የተቀናጀ፣ ባለብዙ ዘርፍ ትብብር ችግሮችን ለመፍታት ያለውን ወሳኝ ሚና አጉልተው ገልጸው በማህበረሰቡ ውስጥ ላሉ ልጆች እና ቤተሰቦች የተቀናጀ እና ዘላቂ የድጋፍ ስርዓቶችን ለመገንባት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።  

photo_2026-01-16_13-50-01
News

የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ (Ethiopian Autism Society) ስራውን በይፋ ጀመረ!

የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ የመጀመሪያውን የዳይሬክተሮች ቦርድ ስብሰባ በትናንትናው ዕለት ( 14/5/2018) የተደረገ ሲሆን በማድረግ፣ ማህበሩን አደረጃጀት ለማጠናከር እና ህጋዊ ሰዉነት ለማግኘት አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች እንዲሁም ከአጭር እና ረጅም ግዜ አኳያ መሰራት በሚገቡ ስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
 
የቦርድ አባላትና የስራ ድልድል አስመልክቶ ፡ ሶሳይቲው የኢትዮጵያን አገር አቀፍ የኦቲዝም ዘርፍ በብቃት ለመምራት ሀሉም የዳይሬክሮች ቦርድ አባላት ከፍተኛ ሀላፊነት የሚጠበቅ ሲሆን የሚከተሉትን የሃላፊነት ጉዳዮችን በመለየት ምደባዎችን አድርጓል።
 
በዚህም መሰረት፣
1. ወ/ሮ እሌኒ ዳምጠው – ሰብሳቢ
2. ወ/ሮ ትዕግስት ሀይሉ – ም/ሰብሳቢ
3. አቶ መንግስቱ ወልዴ – ጸሃፊ፣
4. የተከበሩ ዶ/ር ታደለ ጩማሮ – ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት – የፌዴራል እና ፖሊሲ ጉዳዮች አስተባባሪ፣
5. ዶ/ር አሊ ሳኒ – የቴክኒካል እና ሙያዊ ጉዳዮች አስተባባሪ፣
5. ዶ/ር ዳዊት ዳንኤል – የክልሎች ጉዳይ አስተባባሪ፣
6. ጋዜጤኛ መላኩ ብርሃኑ – የኮሚኒኬሽን እና ሚዲያ ጉዳዮች አስተባባሪ፣
7. ወ/ሮ ልያ ተስፋዬ – የስልጠናዎች እና ካዉንስሊንግ ጉዳይ አስተባባሪ፣
8. ወ/ሮ ራሄል አባይነህ – የወላጆች ጉዳይ አስተባባሪ፣
8. አቶ ኤርሚያስ ሙላቱ- ከጤና ሚኒስቴር – አባል
9. አቶ ሲሳይ ጥላሁን – ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር – አባል
10. አቶ ሄኖክ ሀይሉ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ – አባል
11. ዶ/ር አብዱልዋሃድ አሊ- ከወላጅ- አባል
12. ወ/ሮ መሰረት በቀለ – ከትምህርት ሚ/ር – አባል አባል
13. ወ/ሮ እምዬ ቢተው- ከስራ እና ክሎት ሚ/ር – አባል
15. ወ/ሮ ገነት ንጉሴ – አባል
16. ወ/ሮ ኩለን ኢብራሂም- አባል
17. ወ/ሮ ጥሩወርቅ ተስፋዬ- ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን – የአደረጃጀት ጉዳይ አማካሪ አድርጎ ሰይሟል።
 
የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ የመጀመሪያውን የዳይሬክተሮች ቦርድ ስብሰባ በትናንትናው ዕለት ( 14/5/2018) የተደረገ ሲሆን በማድረግ፣ ማህበሩን አደረጃጀት ለማጠናከር እና ህጋዊ ሰዉነት ለማግኘት አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች እንዲሁም ከአጭር እና ረጅም ግዜ አኳያ መሰራት በሚገቡ ስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
 
የቦርድ አባላትና የስራ ድልድል አስመልክቶ ፡ ሶሳይቲው የኢትዮጵያን አገር አቀፍ የኦቲዝም ዘርፍ በብቃት ለመምራት ሀሉም የዳይሬክሮች ቦርድ አባላት ከፍተኛ ሀላፊነት የሚጠበቅ ሲሆን የሚከተሉትን የሃላፊነት ጉዳዮችን በመለየት ምደባዎችን አድርጓል።
 
 • ሶሳይቲው በኒያ ፋዉንዴሸን (Nia Foundation) ውስጥ በጊዜያዊነት ቢሮ እንዲኖረው።
• ሶሳይቲው ህጋዊ ሰውነት በአስቸኳይ አግኝቶ ስራውን እንዲያከናዉን አስፈላጊው የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟልተው ፣ የመመስረቻ እና መተዳደሪያ ደንብ ሰነዶች ፣ የቦርድ አባላት ተግባር እና ሃላፊት (Job Description) ሰነዶች ተጠናቀው ለቀጣይ ስብሳባ እንዲቀርብ እና ጸድቀው ወደ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ከማመልከቻ ጋር ጥያቄ እንዲቀርብ፣
• በኢትዮጵያ በኦቲዝም ላይ የሚሰሩ ሁሉም ተቋማትና ድርጅቶች እንዲሁም ቤተሰቦች፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና አጋሮች በጋራ በመሆን የኦቲዝም ተሟጋቾችን ድምጽ ከፍ ለማድረግ መጪውን ዓለም አቀፍ የኦቲዝም ግንዛቤ ወር (April 2026) በልዩ ሁኔታ በጋራ ለማክበር ተወስኗል። በዚህም መሠረት፡ April 2/2026 – የኢትዮጵያ የኦቲዝም ግንዛቤ ቀን በአገር አቀፍ ደረጃ በደማቅ ሁኔታ በጋራ ለማክበር እና የመጀመሪያው “Ethiopian Autism Summit- 2026 ” ዝርዝር ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ለቦርዱ እንዲቀርብ ።
• የሶሳይቲው አባላት ማፍራት ላይ በክልል የሚገኙ ድርጅቶች እና ቤተሰቦች ተደራሸ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ እና አባላት የሶሳይቲው አባል በመሆናቸው የሚያገኙት ጥቅሞች ላይ ዝርዝሩ ታይቶ የመመስረቻ ሰነዱ አካል እንዲሆን፣
• የተቋማት እና የኦቲዝም ማዕከላት በመዘዋወር ጉብኝት ማድረግ የሚገኙበትን ሁኔታ የአገልግሎት ደረጃቸውን፣ የልምድ ልዉዉጥ እንዲደረግ እና ማበረታታት እንዲቻል በተከታታይ እንዲደረግ ፕሮግራም እንዲወጣ እና ለቦርዱ እንዲቀርብ፣
• የሶሳይቲው የብራንዲንግ እና የሎጎ ዲዛይን፣ የዌብሳይት ዝግጅት እና ተያያዥ ጉዳዮች የኢትዮጵያን ኦቲዝም ሁኔታ እና የጋራ ድምጻችንን ማመላከት በሚችል መልኩ በጥንቃቄ እንዲሰሩ ሙያዊ እገዛም እንዲደረግ፣ ዉሳኔዎች ተላልፈዋል።
ቀጣይ የዳይሬክተሮች ቦርድ ስብሰባ ፣
አርብ (ጃንዋሪ 30/2026) ከጠዋቱ 5:00-6:00 በኒያ ፋዉንዴሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲደረግ ቀጠሮ ተይዟል።
አብረን በመስራት ፣ ለኦቲዝም ልጆቻችንና ለቤተሰቦቻቸው የተሻለች ኢትዮጵያን እንፈጥራለን!
እናመሰግናለን!
 
615945739_869414392512392_9214619339112551082_n
EventsNews

የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ ምስረታ እዉን ሆነ!

ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ ምስረታ መድረክ በኢሊሌ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ለረጅም ዘመናት ስንሻው የቆዬው ሁሉንም በኦቲዝም ዙሪያ የሚሰሩ ድርጅቶች እና ማህበራት፣ ባለሙያዎች እና ቤተሰቦች እንዲሁም በጉዳዩ ፍላጎት ያላቸውን ባለድርሻ አካላት የሚያቅፍ ሀገር አቀፍ የኦቲዝም ሶሳይቲ ምስረታ እዉን ሆኗል። ሶሳይቲውን የሚመሩ 13 አባላት ያሉት የዳይሬክተሮች ቦርድ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ ይህን ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ማህበር የማደራጀት ከፍተኛ ሀላፊነት በጉባኤው ተሰጥቷል።

የኢትየጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት

1. ወ/ሮ እሌኒ ዳምጠው : ከኒያ ፋዉንዴሽን

2. ወ/ሮ ትዕግስት ሀይሉ : ከምሉዕ ፋዉንዴሸን

3. ወ/ሮ ገነት ንጉሴ : ከቤቴል አዳማ ኦቲዝም ማዕከል

4. ወ/ሮ ኩለን ኢብራሂም : የኛ ልጆች ኦቲዝም ማህበር

5. አቶ ኤርሚያስ ሙላቱ፡ ከጤና ሚኒስቴር

6. አቶ ሲሳይ ሀይሉ: ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

7. ወ/ሮ ጥሩ ወርቅ ተስፋዬ፡ ከሲቪል ማህበረሰቦች ድርጅት ባለስልጣን

8. ዶ/ር ዳዊት ዳንኤል ፡ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል

9. ጋዜጠኛ መላኩ ብርሃኑ ፡ የኦቲዝም በጎ ፈቃድ አምባሳደር (ከነህሚያ ኦቲዝም ማዕከል)

10. ዶ/ር አብዱልዋሃድ አሊ፡ ወላጅ

11. ወ/ሮ ልያ ተስፋዬ ፡ ወላጅ

12. ዶ/ር አሊ ሰኒ ፡ ከአካዳሚያ (አማካሪ)

13. ረ/ፕ ሄኖክ ሀይሉ ፡ ከአካዳሚያ (ከአዲስ አበባ የኒቨርሲቲ) ናቸው

ይህ ለሀገራችን ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ዜና ነው። የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ መመስረት በኦቲዝም ዙሪያ የሚሰሩ ተቋማትን፣ ባለሙያዎችን እና ወላጆችን በአንድ ጥላ ስር በማምጣት የተበታተነውን ጥረት ወደ ላቀ ውጤት እንደሚያሸጋግረው ጥርጥር የለውም።

የተመረጡት የቦርድ አባላት ስብጥርም ከመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ፣ ከሚዲያ፣ ከምሁራን እና ከራሳቸው ከወላጆች መሆኑ ሶሳይቲው ሁሉን አቀፍ እውቀትና ድጋፍ እንዲኖረው ያደርገዋል።

የዚህ ሶሳይቲ መመስረት የሚኖረው ዋና ዋና ጥቅሞች፦

የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳረፍ፦ በኦቲዝም ዙሪያ ያሉ ችግሮችን ለመንግስት አካላት በአንድ ድምፅ በማቅረብ የተሻሉ ህጎች እና መመሪያዎች እንዲወጡ ማድረግ።

ግንዛቤ መፍጠር፦ በህብረተሰቡ ዘንድ ስላለው የተሳሳተ አመለካከት በሰፊውና በሳይንሳዊ መንገድ መስራት።

ልምድ ልውውጥ፦ የተለያዩ ማዕከላትና ባለሙያዎች ያላቸውን ምርጥ ተሞክሮ እንዲለዋወጡ መንገድ መክፈት።

ለወላጆች ድጋፍ፦ ወላጆች መረጃ የሚያገኙበትና እርስ በእርስ የሚደጋገፉበት ጠንካራ መድረክ መፍጠር።

ኒያ ፋውንዴሽን እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እያለ ለማለት ለተመረጡት የቦርድ አባላትም ይህን ትልቅ አገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ብርታቱንና ስኬቱን ይመኝላቸዋል።

photo_2026-01-16_13-50-01
EventsNews

በኦቲዝም ድጋፍ ዙሪያ አጋዥ የሆኑ 2 ማንዋሎች ይፋ ተደረጉ።

በኒያ ፋዉንዴሽን እና በአጋር አካላት የተዘጋጁ ፣ በኦቲዝም ላይ ለሚሰሩ ድርጅቶች፣ የመንግስት አካላት ፣ ባለሙያዎች እና ወላጆች ጠቃሚ የሆኑ ሁለት የህትመት ዉጤቶች ይፋ ተደርገዋል።

የመጀመሪያ ፈታኙን የኦቲዝም ወጣቶች የስነ ተዋልዶ ጤና ጉዳዮች አስመልክቶ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል አጋዥ ማንዋል ሲሆን ሁለተኛው የቤት ለቤት እና ማህበረሰብ አቀፍ የኦቲዝም ተሃድሶ እና ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል አጋዥ የሆነ ማንዋል ነው።

እነዚህ ማንዋሎች በወ/ሮ ዘሚ የኑስ የተጀመሩ ስራዎች ወደ መጠናቀቅ እንዲደርስ ያደረጉ እና በአገራችን ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የመጣዉን የኦቲዝም ሁኔታ ላይ ድጋፍ ለማድረግ እጅግ ወሳኝ መሆናቸው ተጠቁሟል።

እነዚህ አዳዲስ የማስተማሪያ ማንዋሎች (Manuals) ይፋ መደረጋቸው፣ አዲስ ከተመሰረተው የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ ዜና ጋር ተዳምሮ በዘርፉ ትልቅ እምርታ የታየበት ወቅት መሆኑን ያሳያል። በተለይም በወይዘሮ ዘሚ የኑስ የተጀመሩ ራዕዮች ፍሬ አፍርተው ለዚህ መብቃታቸው ለስራው ቀጣይነት ትልቅ ትርጉም ያለው ነው።

የእነዚህ ህትመቶች ዋና ፋይዳ፣

#የኦቲዝም ወጣቶች ስነ-ተዋልዶ ጤና አጋዥ ማንዋል፡ ይህ ርዕሰ ጉዳይ ብዙ ጊዜ በማህበረሰባችን ውስጥ በግልጽ የማይወራ ቢሆንም፣ ኦቲዝም ያለባቸው ወጣቶች ለአካላዊ እና ስነ-ልቦናዊ ለውጦች የሚገባቸውን ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ ወሳኝ ነው። ወላጆች እና ባለሙያዎች ወጣቶቹን እንዴት ማስተማር እና መጠበቅ እንዳለባቸው ሳይንሳዊ እና ባህላዊ ሁኔታን ያገናዘበ መመሪያ ይሰጣል።

#የኦቲዝም ወጣቶች ስነ-ተዋልዶ ጤና አጋዥ ማንዋል፡ ይህ ርዕሰ ጉዳይ ብዙ ጊዜ በማህበረሰባችን ውስጥ በግልጽ የማይወራ ቢሆንም፣ ኦቲዝም ያለባቸው ወጣቶች ለአካላዊ እና ስነ-ልቦናዊ ለውጦች የሚገባቸውን ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ ወሳኝ ነው። ወላጆች እና ባለሙያዎች ወጣቶቹን እንዴት ማስተማር እና መጠበቅ እንዳለባቸው ሳይንሳዊ እና ባህላዊ ሁኔታን ያገናዘበ መመሪያ ይሰጣል።

#የቤት ለቤት እና ማህበረሰብ አቀፍ ተሃድሶ ማንዋል፦ ሁሉም የኦቲዝም ህፃናት ወደ ማዕከላት የመሄድ ዕድል በማያገኙበት ሁኔታ፣ ይህ ማንዋል ድጋፉን ወደ ቤተሰብ እና መንደር ያወርደዋል።ቤተሰቦች በቤታቸው ውስጥ ልጆቻቸውን እንዴት መርዳት እንደሚችሉ ያግዛል፤ እንዲሁም የማህበረሰብ ጤና ሰራተኞች በየደረጃው ድጋፍ እንዲሰጡ አቅም ይፈጥራል።

ህትመቱን እዉን ለማድረግ ድጋፍ ያደረጉ የጊዳቦ ፖሊሲ ማዕከል፣ የፓካርድ ፋዉንዴሸን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ ባለሙዎች እና ቴክኒካል አድቫይዘሮች ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን!

photo_2026-01-16_13-49-53
EventsNews

ከኦቲዝም በማገገም ዩኒቨርሲቲ የደረሰው ወጣት ዳንኤል ኤፍሬም አስደናቂ ንግግር እና ምስክርነት

ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲ ምስረታ መድረክ በኢሊሌ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ለረጅም ዘመናት ስንሻው የቆዬው ሁሉንም በኦቲዝም ዙሪያ የሚሰሩ ድርጅቶች እና ማህበራት፣ ባለሙያዎች እና ቤተሰቦች እንዲሁም በጉዳዩ ፍላጎት ያላቸውን ባለድርሻ አካላት የሚያቅፍ ሀገር አቀፍ የኦቲዝም ሶሳይቲ ምስረታ እዉን ሆኗል።

በዚህ መድረክ ላይ ታሪኩን ያጋራው ወጣት ዳንኤል ኤፍሬም በኒያ ፋዉንዴሸን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል ዉስጥ ለ3 ዓመታት የኦቲዝም ክትትል እና ድጋፍ የተደረገለት ሲሆን ለዉጥ በማምጣት ዛሬ በሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በመማር ላይ ይገኛል። በጉባኤው ላይ ያቀረበው አስቀናቂ ንግግር እና የህይወት ጉዞ ምስክርነት እነሆ!

የተከበራችሁ የኢፌዲሪ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ኃላፊዎች፣ የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የክልል ክልል ማስተዳድር ተወካዮች፣ ተጋባዝ እንግዶች፣ የኦቲዝም መዕከል መሪዎችና ሠራተኞች፣ ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ውድ ወገኖቼ እና ቤተሰባቸው በዚህ ታሪካዊ ቀን በዚህ የተሰበሰባችሁ ታዳሚያን ሁሉ፤ የእግዚአብሔር ሠላም ይብዛላችሁ፡፡

እኔ ዳንኤል ኤፍሬም እባላለሁ፤ ሃያ አንድ ዓመቴ ሲሆን የጆይ ሴንቴር የኦቲዝም መዕከል የቀድሞ ተማሪ ነኝ፡፡ ከ2002 እስከ 2003 ዓ.ም. የጆይ የኦቲዝም መዕከል ስረዳ ቆይቻለሁ፡፡ በቆይታዬ በተወደደችው በወ/ሮ ዜሚ የኑስ እና በማዕከሉ ድንቅ ሠራተኞች በተደረገልኝ ሙያዊ እገዛ፣ በወላጆቼ ጸሎት እና በእግዚአብሔር ልዩ ቸርነት ከኦቲዝም ችግር ወጥቼ ወደ መደበኛ ትምህርት ቤት ገብቼ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቴን በድል ጨርሻለሁ፤ ለዩኒቨርስቲ መግቢያ የሚሰጠውን ፈተና በእግዚአብሔር እርዳታ አልፌ ዛሬ በዩኒቨርስቲ የኮምፕዩቴር ሳይንስ የ1ኛ ዓመት ተማሪ ነኝ፡፡ ለዚህ ለመብቃቴ ትልቅ ድጋፍ ለሰጡኝ ለወ/ሮ ዜሚ የኑስ እና ለጆይ ኦቲዝም መዕከል ሠራተኞች ልባዊ ምስጋዬን አቀርባለሁ፡፡

በዚህ አጭር ምስክርነቴ የነበረኩበትን ከባድ ችግር፣ ቤተሰቤ በችግሬ ምክንያት የከፈለውን ታላቅ መስዋዕትነት እና በተለይም ጆይ ሴንቴር የኦቲዝም መዕከል ያደረገልኝ ሙያዊ እገዛ እና የፍቅር ሥራ በሕይወቴ የመጣውን ታላቅ ለውጥ ላይ ትኩረት አደርጋለሁ፡፡

ወላጆቼ እንደነገሩኝ የኦቲዝም ችግር የገጠመኝ በሁለት ዓመት ከአራት ወር አከባቢ ነበር፡፡ ችግሩ ከመከሰቱ በፊት እንደ ማንኛውም ጤነኛ ልጅ በደስታ እጫወት ነበር፤ ከወላጆቼ ጋር አወራ እና እግባባ ነበር፤ ራሴን ችዬ እመገብ እና እልብስ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ልጅ ስለነበርኩ ለቤተሰቤ የዓይን ማረፍያና ደስታ ነበርኩ፡፡ በሚያሳዝን ሁኔታ ድንገት በማልረዳው ችግር ውስጥ ገበሁ፤ የኦቲዝም ችግር ከገጠመኝ በኋላ በዕለታዊ ሕይወቴ እየሆኑ የነበሩትን አሳቀቂ ነገሮች፣ በራሴ ላይ አደርግ የነበረው ጎጂ ነገሮች እና ለወላጆቼ ልብ የመጣውን ሐዘንና መከራ እኔ አልረዳውም ነበር፤ ነገር ግን ወላጆቼ ከኦቲዝም ካገገምኩ በኋላ የነገሩኝ በአጭሩ አካፍላለሁ፡፡

ወላጆቼ እንደ ነገሩኝ የኦቲዝም ችግር እንደተከሰተ በድንገት ባህርዬ ተለዋወጠ፤ ደስታዬ ጠፋ፤ ሐዘንተኛ ሆንኩ፤ መናገር አቆምኩ፤ ወላጆቼን በዓይን መየት አቆምኩ፤ ምክንያቱ በማተወቅ ሁኔታ ለብዙ ሰዓታት አለቅስ ነበር፤ ወላጆቼ እንደነገሩኝ ራሴን የሚጎዱ ብዙ ነገሮችን አደርግ ነበር፤

ወላጆቼ የተለያዩ የጤና ባለሙያ እንዲመረምሩኝ አድርገው ነበር፤ ነገር ግን በወቅዱ ስለ ኦቲዝም ብዙ ግንዛቤ ስላልነበረ በዚህ ችግር እየተሰቃየሁ መሆነን ለሁለት ዓመታት ያወቀልኝ ሐኪም አልነበረም፤ ወላጆቼ ለሴኮንድ እንኳን ብቻዬን ሊተውኝ አይችሉም ነበር፤ በተለይ ሌሊት ለብዙ ሰዓታት አለቅስ ስለነበረ እናቴ እኔን ለመንከባከብ ብላ እንቅልፍ አልባ ሌሊት ታሳልፍ ነበር፤ በዚህ አጋጣሚ እናቴን ማመስገን እፍልጋለሁ፡፡

ዛሬም በኦቲዝም ችግር ውስጥ ያሉት ህፃናት፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች በብዙ ችግሮች እንደሚሰቃዩ እረዳለሁ፤ ልቤ እጅግ ያዝንላቸዋል፤ በዚህ የተገኛችሁ የመንግሥት አካላት ይህንን በልባችሁ እንድትይዙ አደራ እላለሁ፡፡ በኦቲዝም ችግር ውስጥ መሆነ የታወቀው ከወላጆቼ ጋር ወደ ሲንጋፖር በሄድኩበት ወቅት በተደረገልን ምርመራ ነበር፤ ከዚያ እንደተመለስን ወላጆቼ ወደ ጆይ ኦቲዝም መዕከል ወሰዱኝ፤ ውድ እናታችን ዜሚ ዬኑስ ችግሬን አይታ እጅግ አዘነችልኝ፤ በአስቸኳይ ወደ መዕከሉ ገብቼ ሙያዊ እገዛ እንዳገኝ ወሰነች፤ ለዚህም መልካም ሥራዋ መታሰቢያዋ የተባረከ ይሁን፡፡

በጆይ ኦቲዝም መዕከል በነበርኩበት ሁለት ዓመታት ተዓምራዊ ለውጥ በሕይወቴ ተከሰተ፤ በየዕለቱ በሚደረግልኝ ሙያዊ እገዛ ቀስ በቀስ ቃላትን ማውጣት ቻልኩ፤ ከዚያም አጭር ዐረፍተ ነገሮችን መናገር ጀመርኩ፤ ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ አስቸጋሪ ባህርያቴ ተለወጠ፤ ራሴን መመገብና ማልበስ ቻልኩ፤ ራሴን ችዬ መጸዳዳት እና የግል ንጽህናዬን መጠበቅ ቻልኩ፤ በመጨረሻም መፃፍ እና መንባብን አስተማሩኝ፡፡

በእነዚያ ወሳኝ ሁለት ዓመታት በጆይ ኦቲዝም መዕከል በተደረገልኝ ሙያዊ እገዛ እና እንክብካቤ ሕይወቴ ተለወጠ፤ ወላጆቼ እረት አገኙ፤ እኔም የተለመደ ኑሮ መኖር እና ትምህርቴን እንደ ሌሎች ልጆች ተምሬ ለነገ ሕይወቴ ራሴን እያዘጋጀሁ እገኛለሁ፡፡ በሀገራችን ያሉት ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩት ልጆች ሁሉ እኔ በጆይ የኦቲዝም መዕከል ያገኘሁትን ዓይነት ሙያዊ እገዛ ቢያገኙ በሕይወታቸው ትልቅ ለውጥ እንደሚመጣ እና እኔ የደረሰኩበት ቦታ ሊደርሱ እንደሚችሀሉ አምናለሁ፡፡

ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት የኦቲዝም ማዕከላትን በማስፋፋትና ያሉትንም በበቂ ሁኔታ በመደገፍ የእነዚህን ድንቅ ልጆች ሕይወት የመቀየር ዘላቂ ሥራ እንድትሠሩ አደራ እላለሁ፤ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ መብት የሆነውን የትምህርት ዕድል፣ የጤና እና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩት ልጆች ተደራሽ በማድረግ ራሳቸውን የሚችሉ አምራች ዜጎች እንድታደርጉአቸው በእግዚአብሔር ስም በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

ስላዳመጣችሁኝ አመሰግናለሁ፡፡

417498192_375623571891479_3851587753416173510_n
Events

Invitation to a National Consultative Workshop

Invitation to a National Consultative Workshop on the Establishment of
“National Autism Society of Ethiopia” and the Launch of “Home-Based Autism Rehabilitation &Care”and”SRH
Resource Manual for Professional Working with ASD” Manuals.

photo_2025-12-20_19-36-06
News

የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ክብርት እታገኝ ኃይለማርያም ከኦቲዝም ጋር አብረው የሚኖሩ ህፃናት እና እናቶችን ለመደገፍ ከኒያ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር እንደሚሰሩ አስታወቁ።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በርካታ ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ህፃናት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ እና ስኬታማ እንዲሆኑ የቅርብ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ክብርት ከንቲባ ጠቁመዋል።ዛሬ የተደረገው የፊርማ ስነስርዓት እና የድጋፍ ማእቀፍ የእናቶችን እምባ ያበሰ እና የህፃናትን ተስፋ ያለመለመ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ገልፀዋል።

photo_2025-12-20_19-32-37
News

ኒያ ፋውንዴሽን /ጆይ ኦቲዝም ማዕከል/ ለኦትስቲክ ልጆች እናቶች የመነሻ ካፒታል ርክክብ ተደረገ።

ኒያ ፋውንዴሽን /ጆይ ኦቲዝም ማዕከል/ ለኦትስቲክ ልጆች እናቶች አቅም ግንባታ የመነሻ የሚሆን ካፒታል በዛሬው እለት ርክክብ ተደረገ።

Solverwp- WordPress Theme and Plugin