ዲሰምበር 4 25 ወላይታ ሶዶ
ክብርት ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ከኦቲዝም ጋር አብሮ የሚኖሩ ህፃናት ያላቸውን እናቶች ወደ ስራ እንቅስቃሴ ለማስገባት ልዩ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ገልፀዋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ በርካታ ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ህፃናት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ እና ስኬታማ እንዲሆኑ የቅርብ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ክብርት ከንቲባ ጠቁመዋል።ዛሬ የተደረገው የፊርማ ስነስርዓት እና የድጋፍ ማእቀፍ የእናቶችን እምባ ያበሰ እና የህፃናትን ተስፋ ያለመለመ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ገልፀዋል።
ወይዘሮ እሌኒ ዳምጠው የ ኒያ ፋውንዴሽን ኤግዜኪዩቲቭ ዳይሬክተር በበኩላቸው እናቶችን በማብቃት ኦቲስትክ የሆኑ ህፃናት የተሻለ እጣ ፋንታ እንዲኖራቸው ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል። ጥረታቸው ፍሬያማ ሆኖ ህፃናት ወደ ትምህርት ገበታ እየገቡ እና ከህብረተሰቡ ጋርም እየተቀላቀሉ መሆኑን አስታውቋል። ወይዘሮ እሌኒ ድጋፍ አድርጎ ስራ ማስጀመሪያ መርሀግብር ፕሮግራም በቀጣይ ለሚገነባው የኦቲዝም ማዕከል ምቹ መደላድል እንደሚፈጥርም አብራርተዋል ።ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ህፃናት ያላቸው ወላጆች አርአያ እንዲሆኑ እና ከሌሎች እናቶች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ ወይዘሮ እሌኒ ምክራቸውን ሰጥተዋል።
በኒያ ፋውንዴሽን አቶ የፕሮግም ዳሬክተር የሆኑት አቶ መንግስቱ ወልዴ ለወላጆች ስራ ማስጀመሪያ የሚሆን እና ጥሪት መፍጠሪያ ድጋፍ መደረጉን አስረድተው እናቶችን በማህበር በማደራጀት የመስሪያ ቦታ እና ካፒታል ተመቻችቶላቸው በከተማ ግብርና እንዲሰማሩ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። ኒያ ፋውንዴሽን ከ24 አመት በፊት እንደተመሰረተ የገለፁት የፕሮግም ዳሬክተሩ አቶ መንግስቱ ልጆችን ማካተት እና ማገዝ በእጅጉ አስፈላጊ ስለመሆኑ አስገንዝበዋል።




በፊሪማ ስነ ስርአቱ ላይ ከልባም ኦቲዝም ማዕከል ወጣት ለምለም ንጋቱ የተገኘች ሲሆን ግንዛቤ በመፍጠር እና ልዩ ልዩ ድጋፍ በማድረግ ችግሮችን ለመቋቋም እየተሰራ ነው ብለዋል። የድጋፍ ተጠቃሚ የሆኑ እናቶች በሰጡት አስተያየት ያገኙትን እድል በመጠቀም ሰርተው ለመለወጥ እና ለልጆቻቸው አስፈላጊውን እገዛ ለማድረግ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል።











